ትኩስ ህመም ሳር ቅጠሉ በተኛበት ሰብዓዊ በሞተበት ቤት ደጃፉን በዘጋበት አልጋ ሰውን ባዘለበት በዛች ቅጽበት በዛች ጊዜ . . . ጉብዝና ያላቸው ሙላ አካል የያዙ አካልሽን ተካፍለው ባንቺ ስም የገዙ አዕምሮኣቸው ሰሎ የተጎነደሹ እንዲያ የቆሸሹ ለመጽዳት . . . ዱሻቸውን ታጥበው በዱሽ ተመገቡ ደግሞ አንቺን ዳሰሱሽ ነክተው አቆሸሹሽ በቁራጣ እጃቸው አንቺን አረከሱሽ በዱሽ ደግሞ አጠቡሽ ተነሳ ቅርፊትሽ ውበት ደም ግባትሽ . . . ተጣሰ ህግጋትሽ ጉልበታቸው ሳይዝል ጉልበታም እንዳሉ አዕምሯቸው ደክሞ ማሰብ እንዳልቻሉ እጆች እያላቸው በዱሽ አንቺን በሉ አንቺንም አበሉ ያለ ፍላጎትሽ ያለ አንዳች መሻትሽ በዱሽ ጎረስሽና ሳትረኪ ጠገብሽ ይኸው ገፍ ሆድሽ ያመኛል አሞኛል ታምሜያለው እያልሽ. . . ምግቡ የገባበትን ጉሮሮ እየቧጠጥሽ ትተንፍሺ ዘንድ እንዲያስመልስሽ ቧጠሽ አስወግደሽ ሌላ ትኩስ ህመም ህመምሽ ላይ ጨመርሽ ሌላ ትኩስ አፈር ካፈር ጋር ቀላቀልሽ። 20/6/2008 ዓ.ም